ශුද්ධවූ අල් කුර්ආන් අර්ථ කථනය - අම්හාරික් පරිවර්තනය - අප්‍රිකානු අකාඩමිය

පිටු අංක:close

external-link copy
62 : 2

إِنَّ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَٱلَّذِينَ هَادُواْ وَٱلنَّصَٰرَىٰ وَٱلصَّٰبِـِٔينَ مَنۡ ءَامَنَ بِٱللَّهِ وَٱلۡيَوۡمِ ٱلۡأٓخِرِ وَعَمِلَ صَٰلِحٗا فَلَهُمۡ أَجۡرُهُمۡ عِندَ رَبِّهِمۡ وَلَا خَوۡفٌ عَلَيۡهِمۡ وَلَا هُمۡ يَحۡزَنُونَ

62. እነዚያ በአላህ ያመኑ፣ እነዚያ አይሁዳውያን፣ ክርስቲያኖችና ሳቢያኖችም ሁሉ ከእነርሱ መካከል በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመኑና መልካምን ስራ የሰሩ ሁሉ በእነርሱ ላይ (ምንም ይደርስብናል ብለው) ፍርሀት የለባቸዉም። (ምንም ነገር ያመልጠናል ብለው) አያዝኑምም። info
التفاسير:

external-link copy
63 : 2

وَإِذۡ أَخَذۡنَا مِيثَٰقَكُمۡ وَرَفَعۡنَا فَوۡقَكُمُ ٱلطُّورَ خُذُواْ مَآ ءَاتَيۡنَٰكُم بِقُوَّةٖ وَٱذۡكُرُواْ مَا فِيهِ لَعَلَّكُمۡ تَتَّقُونَ

63. (የኢስራኢል ልጆች ሆይ!) ከበላያችሁ የጡርን ተራራ ያነሳን ሆነን « (ከእሳት ቅጣት) ትጠበቁ ዘንድ የሰጠናችሁን በርትታችሁ ያዙ:: በውስጡ ያለውን ነገር አስታውሱ።» ብለን የጠበቀ ቃል ኪዳናችሁን በያዝንበት ጊዜ የሆነውን ታሪክ (ልብ በሉ)። info
التفاسير:

external-link copy
64 : 2

ثُمَّ تَوَلَّيۡتُم مِّنۢ بَعۡدِ ذَٰلِكَۖ فَلَوۡلَا فَضۡلُ ٱللَّهِ عَلَيۡكُمۡ وَرَحۡمَتُهُۥ لَكُنتُم مِّنَ ٱلۡخَٰسِرِينَ

64. ከዚያም ከዚህ በኋላ ቃልኪዳኑን ተዋችሁ:: በእናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ በትክክል ከጠፊ ህዝቦች በሆናችሁ ነበር። info
التفاسير:

external-link copy
65 : 2

وَلَقَدۡ عَلِمۡتُمُ ٱلَّذِينَ ٱعۡتَدَوۡاْ مِنكُمۡ فِي ٱلسَّبۡتِ فَقُلۡنَا لَهُمۡ كُونُواْ قِرَدَةً خَٰسِـِٔينَ

65. እነዚያም ከናንተ መካከል በቅዳሜ ቀን አሳን በማጥመድ ወሰን ያለፉትንና ለእነርሱም «ወራዳዎች ዝንጆሮዎች ሁኑ።» ያልናቸውን ሕዝቦች ታሪክ በእርግጥ አወቃችሁ። info
التفاسير:

external-link copy
66 : 2

فَجَعَلۡنَٰهَا نَكَٰلٗا لِّمَا بَيۡنَ يَدَيۡهَا وَمَا خَلۡفَهَا وَمَوۡعِظَةٗ لِّلۡمُتَّقِينَ

66. የመንደሯን ሰዎች ቅጣትም ለእነዚያ በጊዜያቸው ለነበሩትና ለእነዚያም ከበኋላቸው ለሚመጡት ሕዝቦች መቀጣጫ ለፈራሂያንም (ትምህርት) አደረግናት። info
التفاسير:

external-link copy
67 : 2

وَإِذۡ قَالَ مُوسَىٰ لِقَوۡمِهِۦٓ إِنَّ ٱللَّهَ يَأۡمُرُكُمۡ أَن تَذۡبَحُواْ بَقَرَةٗۖ قَالُوٓاْ أَتَتَّخِذُنَا هُزُوٗاۖ قَالَ أَعُوذُ بِٱللَّهِ أَنۡ أَكُونَ مِنَ ٱلۡجَٰهِلِينَ

67. (የኢስራኢል ልጆች ሆይ!) ሙሳ ለህዝቦቹ «አላህ ላም እንድታርዱ ያዛችኋል» ባለም ጊዜ (የሆነውን ታሪክ አስታውሱ)። እነርሱም ለሙሳ «መሳለቂያ ታደርገናለህን?» አሉት። እሱም «ከተሳላቂዎች ከመሆን በአላህ እጠበቃለሁ» አላቸው። info
التفاسير:

external-link copy
68 : 2

قَالُواْ ٱدۡعُ لَنَا رَبَّكَ يُبَيِّن لَّنَا مَا هِيَۚ قَالَ إِنَّهُۥ يَقُولُ إِنَّهَا بَقَرَةٞ لَّا فَارِضٞ وَلَا بِكۡرٌ عَوَانُۢ بَيۡنَ ذَٰلِكَۖ فَٱفۡعَلُواْ مَا تُؤۡمَرُونَ

68. እነርሱም «እስቲ ጌታህን ጠይቅልን:: እርሷ ምን እንደሆነች (እድሜዋን) ያብራራልን ዘንድ» አሉ:: እርሱም «‹እርሷ በውልም ያላረጀች ጥጃም ያልሆነች በዚህ መካከል ልከኛ የሆነች ጊደር ናት።› ይላችኋል። የታዘዛችሁትንም ስሩ።» አላቸው። info
التفاسير:

external-link copy
69 : 2

قَالُواْ ٱدۡعُ لَنَا رَبَّكَ يُبَيِّن لَّنَا مَا لَوۡنُهَاۚ قَالَ إِنَّهُۥ يَقُولُ إِنَّهَا بَقَرَةٞ صَفۡرَآءُ فَاقِعٞ لَّوۡنُهَا تَسُرُّ ٱلنَّٰظِرِينَ

69. እነርሱም “እስቲ ጌታህን እንደገና ጠይቅልን:: መልኳ ምን እንደሚመስል ይገልጽልን ዘንድ” አሉ:: እርሱም “መልኳ ደማቅ ተመልካቾችን የምታስደስት ዳልቻ ላም ናት ይላችኋል” አላቸው፡፡ info
التفاسير: