ශුද්ධවූ අල් කුර්ආන් අර්ථ කථනය - අම්හාරික් පරිවර්තනය - අප්‍රිකානු අකාඩමිය

පිටු අංක:close

external-link copy
38 : 2

قُلۡنَا ٱهۡبِطُواْ مِنۡهَا جَمِيعٗاۖ فَإِمَّا يَأۡتِيَنَّكُم مِّنِّي هُدٗى فَمَن تَبِعَ هُدَايَ فَلَا خَوۡفٌ عَلَيۡهِمۡ وَلَا هُمۡ يَحۡزَنُونَ

38. «ሁላችሁም (አደም፣ ሐዋና ሰይጣን) በአንድ ሆናችሁ ከገነት ወደ (ምድር) ውረዱ አልናቸውም። ከዚያም ከእኔ የሆነ መመሪያ ቢመጣላችሁ መመሪያዬን የተከተሉ በእነርሱ ላይ ስጋትም ትካዜም የለባቸውም። info
التفاسير:

external-link copy
39 : 2

وَٱلَّذِينَ كَفَرُواْ وَكَذَّبُواْ بِـَٔايَٰتِنَآ أُوْلَٰٓئِكَ أَصۡحَٰبُ ٱلنَّارِۖ هُمۡ فِيهَا خَٰلِدُونَ

39. «እነዚያም በመልዕክተኞቻችን የካዱና በራዕያችን ያስተባበሉ ሁሉ ግን እነርሱ በውስጧ ዘውታሪዎች ሲሆኑ የእሳት (ገሀነም) ጓዶች ናቸው።» (አልናቸው።) info
التفاسير:

external-link copy
40 : 2

يَٰبَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ ٱذۡكُرُواْ نِعۡمَتِيَ ٱلَّتِيٓ أَنۡعَمۡتُ عَلَيۡكُمۡ وَأَوۡفُواْ بِعَهۡدِيٓ أُوفِ بِعَهۡدِكُمۡ وَإِيَّٰيَ فَٱرۡهَبُونِ

40. እናንተ የኢስራኢል ልጆች ሆይ! ያችን በእናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬን አስታውሱ:: ቃል ኪዳኔንም ሙሉ:: እኔም ቃልኪዳናችሁን እሞላላችኋለሁና። እኔንም ብቻ ፍሩኝ። info
التفاسير:

external-link copy
41 : 2

وَءَامِنُواْ بِمَآ أَنزَلۡتُ مُصَدِّقٗا لِّمَا مَعَكُمۡ وَلَا تَكُونُوٓاْ أَوَّلَ كَافِرِۭ بِهِۦۖ وَلَا تَشۡتَرُواْ بِـَٔايَٰتِي ثَمَنٗا قَلِيلٗا وَإِيَّٰيَ فَٱتَّقُونِ

41. (እናንተ የኢስራኢል ልጆች ሆይ!) ከናንተ ጋር ያለውን መጽሐፍ እውቅና የሚሰጥ ሆኖ ባወረድኩት (ቁርኣን) እመኑ:: በእርሱም የመጀመሪያ ከሓዲያን አትሁኑ:: በአንቃጾቼ ጥቂት ገንዘብ አትለውጡ:: እኔንም ብቻ ፍሩኝ፡፡ info
التفاسير:

external-link copy
42 : 2

وَلَا تَلۡبِسُواْ ٱلۡحَقَّ بِٱلۡبَٰطِلِ وَتَكۡتُمُواْ ٱلۡحَقَّ وَأَنتُمۡ تَعۡلَمُونَ

42. እውነቱን ከውሸት ጋር አትቀላቅሉ:: እናንተም የምታውቁ ስትሆኑ እውነትን አትደብቁ፡፡ info
التفاسير:

external-link copy
43 : 2

وَأَقِيمُواْ ٱلصَّلَوٰةَ وَءَاتُواْ ٱلزَّكَوٰةَ وَٱرۡكَعُواْ مَعَ ٱلرَّٰكِعِينَ

43. ሶላትን ደንቡን ጠብቃችሁ ስገዱ:: ዘካንም ለተገቢው አካል ስጡ:: ለጌታችሁም ከአጎንባሾች ጋር አጎንብሱ:: (ከሰጋጆች ጋር ስገዱ)። info
التفاسير:

external-link copy
44 : 2

۞ أَتَأۡمُرُونَ ٱلنَّاسَ بِٱلۡبِرِّ وَتَنسَوۡنَ أَنفُسَكُمۡ وَأَنتُمۡ تَتۡلُونَ ٱلۡكِتَٰبَۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ

44. እናንተ መጽሐፍን የምታነቡ ሆናችሁና ሰዎችን በበጎ ስራ እያዘዛችሁ ራሳችሁን በመልካም ምግባር ከማነጽ ትዘነጋላችሁን? አታስተውሉምን? info
التفاسير:

external-link copy
45 : 2

وَٱسۡتَعِينُواْ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ وَإِنَّهَا لَكَبِيرَةٌ إِلَّا عَلَى ٱلۡخَٰشِعِينَ

45.በመታገስና በሶላትም ተረዱ፡፡ እርሷ (ሶላት) በፈሪዎች ላይ እንጂ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት። info
التفاسير:

external-link copy
46 : 2

ٱلَّذِينَ يَظُنُّونَ أَنَّهُم مُّلَٰقُواْ رَبِّهِمۡ وَأَنَّهُمۡ إِلَيۡهِ رَٰجِعُونَ

46. እነዚያ ከጌታቸው ጋር እንደሚገናኙና ወደ እርሱ ተመላሾች መሆናቸውን የሚያረጋግጡ ናቸው። info
التفاسير:

external-link copy
47 : 2

يَٰبَنِيٓ إِسۡرَٰٓءِيلَ ٱذۡكُرُواْ نِعۡمَتِيَ ٱلَّتِيٓ أَنۡعَمۡتُ عَلَيۡكُمۡ وَأَنِّي فَضَّلۡتُكُمۡ عَلَى ٱلۡعَٰلَمِينَ

50. የእስራኤል ልጆች ሆይ! ያችን በናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬንና እኔም በዓለማት ላይ ያበለጥኳችሁ (አባቶቻችሁን በጊዜያቸው ከነበሩት ዓለማት ያበለጥኩዋቸው) መኾኔን አስታውሱ፡፡ info
التفاسير:

external-link copy
48 : 2

وَٱتَّقُواْ يَوۡمٗا لَّا تَجۡزِي نَفۡسٌ عَن نَّفۡسٖ شَيۡـٔٗا وَلَا يُقۡبَلُ مِنۡهَا شَفَٰعَةٞ وَلَا يُؤۡخَذُ مِنۡهَا عَدۡلٞ وَلَا هُمۡ يُنصَرُونَ

48. ማንኛዋም ነፍስ ከሌላዋ ነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን፤ ከእርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን፤ ከእርሷም ቤዛ የማይያዝባትንና እነርሱም በየትኛዉም አካል የማይረዱበትን ቀን ቅጣት ፍሩ (ተጠንቀቁ)፡፡ info
التفاسير: