แปล​ความหมาย​อัลกุรอาน​ - คำแปลภาษาอัมฮารา - โดยอะคาเดมีแอฟริกา

ዐበሰ

external-link copy
1 : 80

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ

1. ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፤ info
التفاسير:

external-link copy
2 : 80

أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ

2. ዓይነስውሩ ወደ እርሱ ስለመጣ። info
التفاسير:

external-link copy
3 : 80

وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ

3. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምን ያሳውቅሃል? ምን አልባትም (ይህ አይነስውር ሰው ካንተ በሚሰማው ምክር ከኃጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል:: info
التفاسير:

external-link copy
4 : 80

أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ

4. ወይም ሊገሰጽና ግሳጼይቱም ልትጠቅመው ይከጀላል:: info
التفاسير:

external-link copy
5 : 80

أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ

5. ያ! ከአላህ የተብቃቃውን ሰውማ፤ info
التفاسير:

external-link copy
6 : 80

فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ

6. አንተ ለእርሱ ትዘጋጃለህ። info
التفاسير:

external-link copy
7 : 80

وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ

7. ባይጥራራ (ባያምን)፤ ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትሆን፤ info
التفاسير:

external-link copy
8 : 80

وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ

8. ያ! እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤ info
التفاسير:

external-link copy
9 : 80

وَهُوَ يَخۡشَىٰ

9. እርሱ አላህን የሚፈራ ሲሆን፤ info
التفاسير:

external-link copy
10 : 80

فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ

10. አንተ ከእርሱ ትዘናጋለህ:: info
التفاسير:

external-link copy
11 : 80

كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ

11. ተከልከል፤ (ቁርኣን) ማስገንዘቢያ ነው:: info
التفاسير:

external-link copy
12 : 80

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ

12. የፈለገ ሰው ሁሉ (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል:: info
التفاسير:

external-link copy
13 : 80

فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ

13. በተከበሩት ጹሑፎች ውስጥ ነው:: info
التفاسير:

external-link copy
14 : 80

مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ

14. ከፍ በተደረገች፤ ንጹህም በተደረገች (ጹሑፍ ውስጥ ነው)። info
التفاسير:

external-link copy
15 : 80

بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ

15. በጸሐፊዎች መላዕክት እጆች (ንጹህ የተደረገ):: info
التفاسير:

external-link copy
16 : 80

كِرَامِۭ بَرَرَةٖ

16. የተከበሩና ታዛዦች በሆኑት ጸሐፊዎች (እጆች)፤ info
التفاسير:

external-link copy
17 : 80

قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ

17. ሰው ተረገመ። ምን ከሓዲ አደረገው? info
التفاسير:

external-link copy
18 : 80

مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ

18. (ጌታው) ከምን ነገር ፈጠረው? info
التفاسير:

external-link copy
19 : 80

مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ

19. (አያስብምን?) ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነዉም:: info
التفاسير:

external-link copy
20 : 80

ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ

20. ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው:: info
التفاسير:

external-link copy
21 : 80

ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ

21. ከዚያም ገደለው:: እንዲቀበርም አደረገው፤ info
التفاسير:

external-link copy
22 : 80

ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ

22. ከዚያ ማንሳቱን በፈለገ ጊዜ ያስነሳዋል:: info
التفاسير:

external-link copy
23 : 80

كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ

23. በእውነት ያንን ጌታው ያዘዘውን ገና አልፈጸመም:: info
التفاسير:

external-link copy
24 : 80

فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ

24. ሰው ወደ ምግቡ ይመልከት፤ info
التفاسير:

external-link copy
25 : 80

أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا

25. እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መሆናችንን፤ info
التفاسير:

external-link copy
26 : 80

ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا

26. ከዚያ ምድርን በደካማ ቡቃያ መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤ info
التفاسير:

external-link copy
27 : 80

فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا

27. በውስጧም እህልን ያበቀልን info
التفاسير:

external-link copy
28 : 80

وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا

28. ወይንም እርጥብ ሳርንም፤ info
التفاسير:

external-link copy
29 : 80

وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا

29. የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤ info
التفاسير:

external-link copy
30 : 80

وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا

30. ጭፍቆች አትክልቶችንም፤ info
التفاسير:

external-link copy
31 : 80

وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا

31. ፍራፍሬንና፤ ገለባንም (ያበቀልን መሆናችንን ይመልከት)። info
التفاسير:

external-link copy
32 : 80

مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

32. ለእናንተም ለእንሰሶቻችሁም መጠቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይህን ሰራን):: info
التفاسير:

external-link copy
33 : 80

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ

33. አደንቋሪይቱ (መከራ) በመጣች ጊዜ፤ info
التفاسير:

external-link copy
34 : 80

يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ

34. ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤ info
التفاسير:

external-link copy
35 : 80

وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ

35. ከእናቱም፤ ከአባቱም፤ (በሚሸሽበት ቀን) info
التفاسير:

external-link copy
36 : 80

وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ

36. ከሚስቱና ከልጁም፤ (በሚሸሽበት ቀን) info
التفاسير:

external-link copy
37 : 80

لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ

37. ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን ከሌላው የሚያብቃቃው ሁኔታ አለው:: info
التفاسير:

external-link copy
38 : 80

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ

38. ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች፤ info
التفاسير:

external-link copy
39 : 80

ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ

39. ሳቂዎችና ተደሳቾች ናቸው:: info
التفاسير:

external-link copy
40 : 80

وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ

40. ፊቶች ደግሞ በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትብያ አለባቸው። info
التفاسير:

external-link copy
41 : 80

تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ

41. ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤ info
التفاسير:

external-link copy
42 : 80

أُوْلَٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ

42. እነዚያ እነርሱ በአላህ ከሓዲያን እና በትዕዛዙ ላይ አመጸኞቹ ናቸው። info
التفاسير: