ಪವಿತ್ರ ಕುರ್‌ಆನ್ ಅರ್ಥಾನುವಾದ - ಅಮ್ಹರಿ ಅನುವಾದ - ಆಫ್ರಿಕಾ ಅಕಾಡೆಮಿ

ಪುಟ ಸಂಖ್ಯೆ:close

external-link copy
171 : 4

يَٰٓأَهۡلَ ٱلۡكِتَٰبِ لَا تَغۡلُواْ فِي دِينِكُمۡ وَلَا تَقُولُواْ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلۡحَقَّۚ إِنَّمَا ٱلۡمَسِيحُ عِيسَى ٱبۡنُ مَرۡيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلۡقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرۡيَمَ وَرُوحٞ مِّنۡهُۖ فَـَٔامِنُواْ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦۖ وَلَا تَقُولُواْ ثَلَٰثَةٌۚ ٱنتَهُواْ خَيۡرٗا لَّكُمۡۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٞ وَٰحِدٞۖ سُبۡحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٞۘ لَّهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلٗا

171. እናንተ የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ:: በአላህም ላይ እውነትን እንጂ አትናገሩ:: የመርየም ልጅ አል መሲህ ዒሳ የአላህ መልዕክተኛ ወደ መርየም የጣላት የሁን ቃሉና ከእርሱ የሆነ መንፈስ ብቻ ነው:: በአላህና በመላዕክተኞቹ እመኑ:: «አማልዕክት ሶስት ናቸው።» አትበሉ:: ተከልከሉ:: ለእናንተ የተሻለ ይሆናልና:: አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው:: ለእርሱም ልጅ ያለው ከመሆን የጠራ ነው:: በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው:: መመኪያነትም በአላህ በቃ:: info
التفاسير:

external-link copy
172 : 4

لَّن يَسۡتَنكِفَ ٱلۡمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبۡدٗا لِّلَّهِ وَلَا ٱلۡمَلَٰٓئِكَةُ ٱلۡمُقَرَّبُونَۚ وَمَن يَسۡتَنكِفۡ عَنۡ عِبَادَتِهِۦ وَيَسۡتَكۡبِرۡ فَسَيَحۡشُرُهُمۡ إِلَيۡهِ جَمِيعٗا

172. አል መሲህ ለአላህ ባሪያ ከመሆን ፈጽሞ አይጸየፍም:: ቀራቢዎች የሆኑ መላዕክትም እንዲሁ ለአላህ ባሪያ ከመሆን ፈጽሞ አይጸየፉም:: ወደ አላህ እርሱን ከመገዛት የሚጸየፉና የሚኮሩ ሁሉ አላህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል:: info
التفاسير:

external-link copy
173 : 4

فَأَمَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ وَعَمِلُواْ ٱلصَّٰلِحَٰتِ فَيُوَفِّيهِمۡ أُجُورَهُمۡ وَيَزِيدُهُم مِّن فَضۡلِهِۦۖ وَأَمَّا ٱلَّذِينَ ٱسۡتَنكَفُواْ وَٱسۡتَكۡبَرُواْ فَيُعَذِّبُهُمۡ عَذَابًا أَلِيمٗا وَلَا يَجِدُونَ لَهُم مِّن دُونِ ٱللَّهِ وَلِيّٗا وَلَا نَصِيرٗا

173. እነዚያ በአላህ ያመኑና መልካም ተግባራትን የሰሩትን ምንዳዎቻቸውን ይሞላላቸዋል:: ከችሮታዉም ይጨምርላቸዋል:: እነዚያን የተጸየፉትና የኮሩትን ግን አሳማሚውን ቅጣት ይቀጣቸዋል:: ከአላህ ሌላ ለእነርሱ ዘመድና ረዳት አያገኙም:: info
التفاسير:

external-link copy
174 : 4

يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ قَدۡ جَآءَكُم بُرۡهَٰنٞ مِّن رَّبِّكُمۡ وَأَنزَلۡنَآ إِلَيۡكُمۡ نُورٗا مُّبِينٗا

174. እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ዘንድ በእርግጥም አስረጅ መጣላችሁ:: ወደ እናንተም ገላጭ የሆነን ብርሃንን (ቁርኣንን) አወረድን:: info
التفاسير:

external-link copy
175 : 4

فَأَمَّا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ بِٱللَّهِ وَٱعۡتَصَمُواْ بِهِۦ فَسَيُدۡخِلُهُمۡ فِي رَحۡمَةٖ مِّنۡهُ وَفَضۡلٖ وَيَهۡدِيهِمۡ إِلَيۡهِ صِرَٰطٗا مُّسۡتَقِيمٗا

175. እነዚያማ በአላህ ያመኑና በእርሱ የተጠበቁ ሰዎች ከእርሱ በሆነው እዝነትና ችሮታ ውስጥ እርግጥ ያስገባቸዋል:: ወደ እርሱም ቀጥተኛ መንገድን ይመራቸዋልም:: info
التفاسير: