Translation of the Meanings of the Noble Qur'an - Amharic translation - Africa Academy

አን ናዚዓት

external-link copy
1 : 79

وَٱلنَّٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا

1. (ነፍስን (ሩህን)) በኃይል መንጫቂዎች በሆኑት፤ info
التفاسير:

external-link copy
2 : 79

وَٱلنَّٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا

2. በቀስታ መምዘዝን መዛዦች በሆኑትም፤ info
التفاسير:

external-link copy
3 : 79

وَٱلسَّٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا

3. መዋኘትንም ዋኚዎች በሆኑት፤ info
التفاسير:

external-link copy
4 : 79

فَٱلسَّٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا

4. መቅደምንም ቀዳሚዎች በሆኑት፤ info
التفاسير:

external-link copy
5 : 79

فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا

5. ጉዳይንም አስተናባሪዎች በሆኑት መላዕክት እምላለሁ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)። info
التفاسير:

external-link copy
6 : 79

يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ

6. (ይህም የሚሆነው) ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤ info
التفاسير:

external-link copy
7 : 79

تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ

7. ተከታይቱም በምትከተላት ቀን (ትቀሰቀሳላችሁ)። info
التفاسير:

external-link copy
8 : 79

قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ

8. በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው:: info
التفاسير:

external-link copy
9 : 79

أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ

9. ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው። info
التفاسير:

external-link copy
10 : 79

يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ

10. «እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ሁኔታ ተመላሾች ነን እንዴ?» ይላሉ። info
التفاسير:

external-link copy
11 : 79

أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ

11. የበሰበሱ አጥንቶች በሆንን ጊዜ እንደገና እንቀሰቀሳለን? info
التفاسير:

external-link copy
12 : 79

قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ

12. «እንዲያማ ከሆነ ያች የኪሳራ መመለስ ናታ!» ይላሉ። info
التفاسير:

external-link copy
13 : 79

فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ

13. እርሷን (እውን የምታደርጋት) አንዲት ጩኸት ብቻ ናት። info
التفاسير:

external-link copy
14 : 79

فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ

14. ወዲያውኑ በንቃት ላይ ናቸው። info
التفاسير:

external-link copy
15 : 79

هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ

15. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሙሳ ወሬ መጣልህን? info
التفاسير:

external-link copy
16 : 79

إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى

16. ጌታው በተቀደሰው ጡዋ ሸለቆ በጠራው ጊዜ፤ info
التفاسير:

external-link copy
17 : 79

ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ

17. ወደ ፈርዖን ሂድ፤ ወሰን አልፏልና:: info
التفاسير:

external-link copy
18 : 79

فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ

18. (እንዲህም) በለው: «እራስህን ለማጥራት ታስባለህን? info
التفاسير:

external-link copy
19 : 79

وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ

19. ጌታህንም ትፈራ ዘንድ መንገዱን ልመራህ፤ (ታስባለህን?)» info
التفاسير:

external-link copy
20 : 79

فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ

20. (ሙሳ ለፈርዖን) ታላቁንም ተዐምር አሳየው። info
التفاسير:

external-link copy
21 : 79

فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ

21. አስተባበለም፤ አመጸም፤ info
التفاسير:

external-link copy
22 : 79

ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ

22. ከዚያ ለመጥፋት የሚተጋ ሆኖ ዞረ:: info
التفاسير:

external-link copy
23 : 79

فَحَشَرَ فَنَادَىٰ

23. (ህዝቡን) ሰበሰበም ተጣራም። info
التفاسير:

external-link copy
24 : 79

فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ

24. እኔ «ታላቁ ጌታችሁ ነኝ» አለም። info
التفاسير:

external-link copy
25 : 79

فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ

25. አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ ቃል ቅጣት ያዘው:: info
التفاسير:

external-link copy
26 : 79

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ

26. በዚህ ውስጥ አላህን ለሚፈሩ በእርግጥ ማስጠንቀቂያ አለበት። info
التفاسير:

external-link copy
27 : 79

ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا

27. በአፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት:: info
التفاسير:

external-link copy
28 : 79

رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا

28. ከፍታዋን አጓነ አስተካከላትም። info
التفاسير:

external-link copy
29 : 79

وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا

29. ሌሊቷንም ሸፈነ፤ ቀኗንም ግልጽ አደረገ። info
التفاسير:

external-link copy
30 : 79

وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ

30. ምድርንም ከዚያ በኋላ ዘረጋት። info
التفاسير:

external-link copy
31 : 79

أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا

31. ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ:: info
التفاسير:

external-link copy
32 : 79

وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا

32. ጋራዎችንም አደላደላቸው። info
التفاسير:

external-link copy
33 : 79

مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ

33. ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጣቀሚያ ይሆን ዘንድ (ይሄን አደረገ)። info
التفاسير:

external-link copy
34 : 79

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ

34. ታላቂቱም መዓት በመጣች ጊዜ፤ info
التفاسير:

external-link copy
35 : 79

يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ

35. ሰው ሁሉ የሰራውን የሚያስታውስበት ቀን፤ info
التفاسير:

external-link copy
36 : 79

وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ

36. ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፤ info
التفاسير:

external-link copy
37 : 79

فَأَمَّا مَن طَغَىٰ

37. የካደ ሰውማ፤ info
التفاسير:

external-link copy
38 : 79

وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا

38. ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፤ info
التفاسير:

external-link copy
39 : 79

فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

39. በእርግጥ መኖሪያው ጀሀነም ናት። info
التفاسير:

external-link copy
40 : 79

وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ

40. በጌታው ፊት መቆምን የፈራና ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለማ፤ info
التفاسير:

external-link copy
41 : 79

فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ

41. በእርግጥ መኖሪያው ገነት ናት። info
التفاسير:

external-link copy
42 : 79

يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا

42. ስለሰዓቲቱም መነሻዋ መቼ እንደሆነ ይጠይቁሃል። info
التفاسير:

external-link copy
43 : 79

فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ

43. (ለመሆኑ አንተ ስለዚያች እለት) በመወሳቷ ምን ላይ አለህበትና? info
التفاسير:

external-link copy
44 : 79

إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ

44. የእርሷ ጉዳይ የሚመለሰው ወደ ጌታህ ብቻ ነው:: info
التفاسير:

external-link copy
45 : 79

إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا

45. አንተ ያለብህ ለሚፈራት ሰው ሁሉ ስለ እርሷ (ከወዲሁ) ማስጠንቀቅ ነው። info
التفاسير:

external-link copy
46 : 79

كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا

46. እነርሱ የሚያይዋት ቀን የአንዲትን ቀን ምሽት ወይም ረፋዷን እንጂ ያልቆዩ ይመስላሉ:: info
التفاسير: